Saturday, March 10, 2012

የአፍሪቃ መሪዎች ዋነኛው ችግር

አበው መጨረሻዬን አሳምርልኝ የሚሏት ነገር አለቻቸው፡፡ መጀመርያው አምሮ መጨረሻው ሲበላሽ እንደማየት የሚያስፈራ ነገር የለምና፡፡ የአያሌ አፍሪካ መሪዎች ዋናው ችግር ሌብነት፣ ስግብግብነት፣ ራስ ወዳድነት፣ ብሔራዊ ስሜት አልባነት፣ ቸልተኝነትና ንቀት ብቻ ሳይሆን መጨረሻን አለመገመትም ነው፡፡


 የተራበ እባብ በቀጭኑ የጠርሙስ አንገት አስግጎ ወተት ወዳለበት የጠርሙስ ሆድ ሲገባ በጣም ይቀለዋል ይባላል፡፡ ሲወጣ ግን ጭንቅ ነው፤ ወተቱን ጠጥቶ ሆዱ ተወጥሯልና፡፡ ምናልባት ያለ ችግር ለመውጣት የጠጣውን ሁሉ መትፋት ይኖርበት ይሆናል፡፡


 ብዙዎቹ የአፍሪካ መሪዎች ከሥልጣን የተገረሰሱትም ሆነ ከሥልጣን ኮርቻ ላይ ያሉት የሕዝባቸው ዕዳ አለባቸው፡፡ የመልካም አስተዳደር ዕዳ፣ የዲሞክራሲ ዕዳ፣ ሀሳቡን በነጻነት ይገልጽ ዘንድ አጨብጭቦ መንበር ላይ ለሰቀላቸው ሰው ዕድል ያለመስጠት ዕዳ፣ ያልተዛባ ፍትህ ዕዳና ወዘተ . . . ለዚህም ነው የብዙዎቹ መጨረሻ እንደ ጅማሬያቸው የማያምረው፡፡ አብዛኞቹ የወተቱ ጠርሙስ ውስጥ እስኪገቡ ድረስ ነው ለሕዝብ የቆሙ የሚመስሉት፡፡

No comments:

Post a Comment

ብዙ ሰዎች አስተየያየት ለመስጠት እንደተቸገሩ ነግረውኛል፤ ነገር ግን ምናልባት ባማራጭነት ከቀረቡልዎ አካውንቶች መካከል እርስዎ የትኛውም ከሌለዎ Comment as Anonymous የሚለውን በመጠቀም በቀላሉ አስተያየትዎን መስጠት ይችላሉ፡፡